Log in
Who is online?
In total there is 0 user online :: 0 Registered, 0 Hidden and 0 Guests :: 1 BotNone
Most users ever online was 11 on Thu Jul 22, 2010 10:46 am
Latest topics
የሰንደቅ ዓላማው ቀን!
Page 1 of 1 • Share •
የሰንደቅ ዓላማው ቀን!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኢትዮጵያ ትውፊት መሠረት በክረምቱ መውጫ በመስከረም 25 ቀን 2002 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ ለሁለተኛ ጊዜ ተከብሯል፡፡
ሐቻምና በፓርላማው የሥራ ጊዜ ማብቂያ ወር የተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን፣ ዘንድሮ ከመክፈቻው ጋር ተያይዞ ተከብሯል፡፡ በዓሉ ቋሚ ቀን ባይኖረውም የበዓሉ ድንበር ግን በአዋጁ ተቀምጧል፡፡
በየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዲሪ) የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001፣ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን የሚከበረው በየዓመቱ መስከረም ሁለተኛ ሳምንት ሰኞ ይከበራል፤ ይላል፡፡ ይህን አዋጅ ከተከተልን በዓሉ መከበር የነበረበት መስከረም 11 ቀን ሰኞ ነበር፡፡ የሁለተኛ ሳምንት ሰኞ እርሱ ነውና፡፡ በነሐሴ መገባደጃና በጳጉሜንም ሆነ በመስከረም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስለ በዓሉ ሲያስተዋውቅ "የሰንደቅ ዓላማ ቀን በመስከረም ሁለተኛ ሳምንት ሰኞ ይከበራል፡፡ በዚህ መሠረት በዓሉ መስከረም 25 ቀን 2002 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ ይከበራል" ብሏል፡፡
መስከረም 25 ቀን ግን 2ኛ ሳምንት ሳይሆን 4ኛውና የመጨረሻው ሳምንት ነው፡፡ ባለፈው ሰኞ የተከበረው በዓሉ ከፓርላማው የሥራ ጊዜ መጀመሪያ ጋር የተገጣጠመ ነው፡፡ በየዓመቱም ሁለቱ ክስተቶች የሚገጥሙ ከሆነ የሰንደቅ ዓላማው አዋጅ የወጣበት ነጋሪት ጋዜጣ አንቀጽ 4 ከኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አዋጅ ቁጥር 1/1987 አንቀጽ 58 ቁጥር 2 ጋር መዋደድ፣ መስማማት ይኖርበታል፡፡ ምክር ቤቱ የሚከፈትበት ጊዜ የመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ላይ መሆኑን ያመለክታልና፡፡
በዓሉ ሲከበር አከባበሩ ሕጉን ጠብቆ የተከተለ ላለመሆኑ አንዳንድ የታዘብናቸው ነጥቦች አሉ፡፡
አንደኛው በተሽከርካሪዎች ላይ ስለሚኖር የሰንደቅ ዓላማ አጠቃቀም ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ በአዋጁ መሠረት በየተሽከርካሪው ላይ የሪፐብሊኩን ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል መጠቀም የሚችሉት ርእሰ ብሔሩ፣ ርእሰ መንግሥቱና አዋጁ የፈቀደላቸው ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ናቸው፡፡ በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች የታየው ግን በየታክሲው፣ በየባጃጁ፣ በየአውቶቡሱና በሌሎች ተሽከርካሪዎች ሲውለበለብ ታይቷል፡፡
ሌላው ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 13 "የሰንደቅ ልሳን" በሚል ንኡስ ርእስ ሥር "የማንኛውም ሰንደቅ ልሳን (ጫፍ) ግማሽ የክብ አምሳል ይኖረዋል" ተብሎ የተጠቀሰው አልተስተዋለም፡፡ ከጦር ምልክት በቀር፡፡
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጥንታዊ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተለይ በ17ኛው ምእት ዓመት የማዕከላዊው መንግሥት መዲና ጎንደር በነበረበት ወቅት የነገሡት አፄ አእላፍ ሰገድ ዮሐንስ ዜና መዋዕል ላይ እንደተፃፈው፣ ንጉሡ ጎጃም ውስጥ ከምትገኘው ደብረ ወርቅ ማርያም ለመታሰቢያ የሰጡዋቸው ሁለት ሰንደቅ ዓላማዎች ቅርፃቸው፣ ይዞታቸው፣ የቀለማቸው ልዩነትና አቀማመጥ ዛሬ ያለውን ዓይነት ነበር፡፡
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን፣ ሰንደቅ ዓላማ ሲወጣና ሲወርድ የሚዘመር መዝሙር ነበር፡፡ ከዘመነ ደርግ ወዲህ ግን ቀርቷል፡፡ ትንሣኤ ይኖረው ይሆን?
በአዲስ አበባ ያኔ የጦር ክፍሎች ባሉበት ባንዲራ ሲወጣና ሲወርድ ጡሩምባ ይሰማ ነበር፡፡ ሲወጣም ሆነ ሲወርድ አንድም ሰው አይነቃነቅም ነበር፤ ከተማው ቀጥ ብሎ ነበር የሚቆመው፡፡ አሁንስ?
ሐቻምና በፓርላማው የሥራ ጊዜ ማብቂያ ወር የተከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን፣ ዘንድሮ ከመክፈቻው ጋር ተያይዞ ተከብሯል፡፡ በዓሉ ቋሚ ቀን ባይኖረውም የበዓሉ ድንበር ግን በአዋጁ ተቀምጧል፡፡
በየኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዲሪ) የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001፣ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን የሚከበረው በየዓመቱ መስከረም ሁለተኛ ሳምንት ሰኞ ይከበራል፤ ይላል፡፡ ይህን አዋጅ ከተከተልን በዓሉ መከበር የነበረበት መስከረም 11 ቀን ሰኞ ነበር፡፡ የሁለተኛ ሳምንት ሰኞ እርሱ ነውና፡፡ በነሐሴ መገባደጃና በጳጉሜንም ሆነ በመስከረም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስለ በዓሉ ሲያስተዋውቅ "የሰንደቅ ዓላማ ቀን በመስከረም ሁለተኛ ሳምንት ሰኞ ይከበራል፡፡ በዚህ መሠረት በዓሉ መስከረም 25 ቀን 2002 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ ይከበራል" ብሏል፡፡
መስከረም 25 ቀን ግን 2ኛ ሳምንት ሳይሆን 4ኛውና የመጨረሻው ሳምንት ነው፡፡ ባለፈው ሰኞ የተከበረው በዓሉ ከፓርላማው የሥራ ጊዜ መጀመሪያ ጋር የተገጣጠመ ነው፡፡ በየዓመቱም ሁለቱ ክስተቶች የሚገጥሙ ከሆነ የሰንደቅ ዓላማው አዋጅ የወጣበት ነጋሪት ጋዜጣ አንቀጽ 4 ከኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አዋጅ ቁጥር 1/1987 አንቀጽ 58 ቁጥር 2 ጋር መዋደድ፣ መስማማት ይኖርበታል፡፡ ምክር ቤቱ የሚከፈትበት ጊዜ የመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ላይ መሆኑን ያመለክታልና፡፡
በዓሉ ሲከበር አከባበሩ ሕጉን ጠብቆ የተከተለ ላለመሆኑ አንዳንድ የታዘብናቸው ነጥቦች አሉ፡፡
አንደኛው በተሽከርካሪዎች ላይ ስለሚኖር የሰንደቅ ዓላማ አጠቃቀም ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ በአዋጁ መሠረት በየተሽከርካሪው ላይ የሪፐብሊኩን ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል መጠቀም የሚችሉት ርእሰ ብሔሩ፣ ርእሰ መንግሥቱና አዋጁ የፈቀደላቸው ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ናቸው፡፡ በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች የታየው ግን በየታክሲው፣ በየባጃጁ፣ በየአውቶቡሱና በሌሎች ተሽከርካሪዎች ሲውለበለብ ታይቷል፡፡
ሌላው ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 13 "የሰንደቅ ልሳን" በሚል ንኡስ ርእስ ሥር "የማንኛውም ሰንደቅ ልሳን (ጫፍ) ግማሽ የክብ አምሳል ይኖረዋል" ተብሎ የተጠቀሰው አልተስተዋለም፡፡ ከጦር ምልክት በቀር፡፡
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጥንታዊ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተለይ በ17ኛው ምእት ዓመት የማዕከላዊው መንግሥት መዲና ጎንደር በነበረበት ወቅት የነገሡት አፄ አእላፍ ሰገድ ዮሐንስ ዜና መዋዕል ላይ እንደተፃፈው፣ ንጉሡ ጎጃም ውስጥ ከምትገኘው ደብረ ወርቅ ማርያም ለመታሰቢያ የሰጡዋቸው ሁለት ሰንደቅ ዓላማዎች ቅርፃቸው፣ ይዞታቸው፣ የቀለማቸው ልዩነትና አቀማመጥ ዛሬ ያለውን ዓይነት ነበር፡፡
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን፣ ሰንደቅ ዓላማ ሲወጣና ሲወርድ የሚዘመር መዝሙር ነበር፡፡ ከዘመነ ደርግ ወዲህ ግን ቀርቷል፡፡ ትንሣኤ ይኖረው ይሆን?
በአዲስ አበባ ያኔ የጦር ክፍሎች ባሉበት ባንዲራ ሲወጣና ሲወርድ ጡሩምባ ይሰማ ነበር፡፡ ሲወጣም ሆነ ሲወርድ አንድም ሰው አይነቃነቅም ነበር፤ ከተማው ቀጥ ብሎ ነበር የሚቆመው፡፡ አሁንስ?

yaredlove- Admin
- Posts: 52
Join date: 2009-07-12
Age: 18
Location: Ethiopia/Nazareth

Page 1 of 1
Permissions in this forum:
You cannot reply to topics in this forum
» Did you know this? ይህን ያውቁ ኖርዋል ?
» ኢትዮጵያ(ኢትዮጵያ የሚለው ስያሜ)
» ፈገግ ...ፈገግ ....ፈገግታ ...ላንድ ..አፍታ !!!
» Men, Love & Sex....
» የእግር ኳስ አጀማመር
» የሰንደቅ ዓላማው ቀን!
» ለማይክል ጃክሰን ሌላ የቀብር ሥነ ሥርዓት
» ቢዮንሴና ጋጋ ለኤም ቲቪ ቁንጮነት ይፎካከራሉ
» ማይክል ጃክሰን ለሞት የሚያደርስ መጠን ያለው መድሃኒት ወስዶ ነበር
» የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ምንጭ ከየት ነው?
» ለታላቁ ሽልማት የበቃው የሚሌኒየሙ ሥነ ጥበብ
» "ሥዕል አደገ፣ አላደገም . . . "
» Photoshop Tutorials In Amharic
» በደመና ውስጥ ባክቴሪያ ተገኘ
» ከ67 አመታት በኋላ የተገኘው የአልማዝ ቀለበት
» ንቦች(በታታሪነት ንቦችም ከጉንዳን የሚተናነሱ አይደሉም)
» ስለ ገንዘብ ከተነገሩ ምሳሌያዊ አነጋገሮች
» ታዳጊው መስማት ከተሳነው ከ9 ዓመታት በኋላ መስማት ቻለ
» የስብሀት ወጎች